የኣማርኛ ፊደል: ፊደል
ኣማርኛ እንደሌላ የዓለም ፊደላት በእራሱ ፊደል ለብዙ ዘመናት በእጅ ሲጻፍ ቆይቶ በ፲፱፻ ዓ.ም. ገደማ በማተሚያ መሣሪያ ሊከተብ ችሏል። ኤውሮፓ ውስጥም ማተሚያ ቤቶች ቀደም ብለው ኣትመውበታል። የግዕዝ ፊደል በዶ/ር ኣበራ ሞላ ፈጠራ ወደ ኮምፒዩተር ገብቶ ከ፲፱፻፹ ዓ.ም. ወዲህ በኮምፕዩተር መጠቀም ከመቻሉም ሌላ በዩኒኮድ ዕውቅና ኣግኝቷል። ይህ የውክፔዲያ ገጽም የቀረበው በእዚሁ ሥርዓት ሲሆን በቋንቋው የተጻፉ መረጃዎች ቊጥር እያደገ ነው።
የዓማርኛ ፊደልና ቋንቋም ዕውቅና እያደገ ስለመጣ በእጅ ስልኮችም በሚገባ ሥራ ላይ እየዋለ ነው። ኣፕል የቋንቋ ገበታዎቹን ሌሎችም እንዲጠቀሙበት በ፳፻፯ ዓ.ም. ስለከፈተ ዓማርኛን እንደሌላ የዓለም ባለፊደል ቋንቋዎች መርጦ መጠቀም ተችሏል።
ዓማርኛ ተራጽሑፍ Amharic Text
የኣማርኛ ፊደል: የውጭ ፡ መያያዣዎች